ከእግዚብሔር ጋር መሆን
…በዳዊት አብርሃም…
አንድ ክርስቲያን ከሁሉ አስቀድሞ ከእግዚአብሔር ጋር ለመሆን ማቀድ ይኖርበታል፡፡ ይህም የተሳካ መንፈሳዊ ሕይወት እንዲኖረው ያስችለዋል፡፡ የተሳካ መንፈሳዊ ሕይወት ደግሞ ለስኬታማ ምድራዊ ሕይወት መሠረት ነው፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን ነጥቦች በመመልከት ለመተግበር መጣር ያስፈልጋል፡፡
- ጸሎት
“ወደፈተና እንዳትገቡ ተግታችሁ ጸልዩ፡፡” ተብለን በተመከርነው መሠረት በግል፣ በቤተሰብና በማኅበር በያንዳንዷ ሥራችን መጀመሪያና መጨረሻ እንዲሁም በማዕድ ስንቀመጥ ልንጸልይ ይገባል፡፡ ጸሎት ከእግዚአብሔርም ጋር የምንሆንበት ዋነኛው መንገድ ነው፡፡ እግዚብሔርም ከእኛ ጋር የሚንሆንበት ዋነኛው መንገድ ነው፡፡ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ ደግሞ ሁሉም ነገር ይከናወንልናልና፡፡ ሌላው ቀርቶ እግዚአብሔር ከርሱ ጋር መሆኑን ማሳብና ማመን የቻለ ሰው ይህን በማሰቡ ብቻ ከፍርሐት ነፃ ይሆናል፡፡ ሰላማዊ መንፈስም ይኖረዋል፡፡